News detail

Image Here

የዘላቂ ልማት ግቦችን ተግባራዊነት ለማጠናከር ባለሙያዎች ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። መጋቢት 2/2017 (ፕ.ል.ሚ - አዲስ አበባ)

ዛሬ በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የዘላቂ የልማት ግቦች የቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር በቀጣይ ስራዎች ላይ ተግባራዊነት ዙሪያ የተደረገው ውይይት ጠቃሚ እንደነበር ተገልጿል።

የቴክኒካል ኮሚቴው አባላት ከፌዴራል ሚኒስቴር አስፈፃሚ የመንግስት ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች፣ ከሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ከግል ዘርፍ የተውጣጡ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት በተቀመጠው ፍኖተ ካርታ በተቀናጀ ስትራቴጂ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን ውይይቱ በኢትዮጵያ የዘላቂ የልማት ግቦች ሁሉን ባካተተ መንገድና በዘላቂነት ውጤታማ ሆኖ እንዲተገበር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

recent News
  • Image Here

    የዘላቂ ልማት ግቦችን ተግባራዊነት ለማጠናከር ባለሙያዎች ተቀናጅተው ሊሰሩ …

    25 June 2026
  • Image Here

    Ministry has confirmed the National Carbon Market Strategy …

    25 June 2026
  • Image Here

    MoPD Launches Ethiopia’s First Regional Economic Accounts Handbook

    25 June 2026