News detail

Image Here

የዘላቂ ልማት ግቦችን ተግባራዊነት ለማጠናከር ባለሙያዎች ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። መጋቢት 2/2017 (ፕ.ል.ሚ - አዲስ አበባ)

ዛሬ በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የዘላቂ የልማት ግቦች የቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር በቀጣይ ስራዎች ላይ ተግባራዊነት ዙሪያ የተደረገው ውይይት ጠቃሚ እንደነበር ተገልጿል።

የቴክኒካል ኮሚቴው አባላት ከፌዴራል ሚኒስቴር አስፈፃሚ የመንግስት ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች፣ ከሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ከግል ዘርፍ የተውጣጡ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት በተቀመጠው ፍኖተ ካርታ በተቀናጀ ስትራቴጂ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን ውይይቱ በኢትዮጵያ የዘላቂ የልማት ግቦች ሁሉን ባካተተ መንገድና በዘላቂነት ውጤታማ ሆኖ እንዲተገበር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

recent News
  • Image Here

    የዘላቂ ልማት ግቦችን ተግባራዊነት ለማጠናከር ባለሙያዎች ተቀናጅተው ሊሰሩ …

    01 February 2026
  • Image Here

    በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተለይም …

    01 February 2026
  • Image Here

    Ethiopia and Vietnam to Strengthen Trade and Investment …

    01 February 2026