Image Here

ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር እ.ኤ.አ. የ2025 የአለም የህዝብ ቁጥር ሪፖርት በሀገር አቀፍ ደረጃ ይፋ በሚደረግበት እና የአለም ህዝብ ቀንን አስመልክቶ በሚደረገው ዝግጅት ላይ ከኢትዮጵያ የUNFPA ተወካይ ሚስተር ኮፊ ኩዋሜ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

አዲስ አበባ | ሰኔ 23/2017 ዓ.ም

ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር እ.ኤ.አ. የ2025 የአለም የህዝብ ቁጥር ሪፖርት በሀገር አቀፍ ደረጃ ይፋ በሚደረግበት እና የአለም ህዝብ ቀንን አስመልክቶ በሚደረገው ዝግጅት ላይ ከኢትዮጵያ የUNFPA ተወካይ ሚስተር ኮፊ ኩዋሜ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱም ወገኖች ቁልፍ የህዝብ እና የልማት ጥያቄዎችን ለመፍታት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። ተጨማሪ የትብብር መስኮችን ላይ ስትራቴጂያዊ አጋርነታቸውን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተነጋግረዋል። ክብርት ዶ/ር ፍፁም እና ሚስተር ኩዋሜ በሚኒስቴሩ እና በUNFPA መካከል ያለው ትብብር ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተስማምተዋል።

recent News
  • Image Here

    ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር …

    04 April 2026
  • Image Here

    ኢትዮጵያ የምዘና ስርአትን በሀገርና በአፍሪካ እንዲስፋፋ ከአፍሪካና ከኢትዮጵያና …

    04 April 2026
  • Image Here

    04 April 2026