ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በፕላንና ልማት ሚኒስቴር ተገኝተዉ ቀጣዩን የህዝብና ቤት ቆጠራ በተመለከተ ገለጻ ተደረገላቸዉ።
***********************************************************************************************
የካቲት 20/2016 አዲስ አበባ (የፕ.ል.ሚ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በፕላንና ልማት ሚኒስቴር ተገኝተዉ ቀጣዩን የህዝብና ቤት ቆጠራ በተመለከተ ገለጻ ተደረገላቸዉ።
በተደረገዉ ገለጻ ቀጣዩ የህዝብና ቤት ቆጠራ የሶስት አመቱ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም አካል መሆኑን ተጠቅሷል። ለህዝብና ቤት ቆጠራዉ የሚከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲሁም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችም ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል። በመጨረሻም ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የስራ መመሪያና አቅጣጫ በመስጠት ዉይይቱ ተጠናቋል።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርን ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል።