Image Here

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከአለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የኢትዮጵያ ተወካይ ቶቢያስ ናይቦ ጋር በጽህፈት ቤታቸዉ ተወያዩ፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከአለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የኢትዮጵያ ተወካይ ቶቢያስ ናይቦ ጋር በጽህፈት ቤታቸዉ ተወያዩ፡፡

*****************************************************************************************************************

የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ(የፕ.ል.ሚ)

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከአለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የኢትዮጵያ ተወካይ ቶቢያስ ናይቦ ጋር በጽህፈት ቤታቸዉ ተወያዩ፡፡

በዉይይታቸዉም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡

በቀጣይ ሶስት አመታት የሚተገበረዉን እና ሰሞኑን ይፋ የሆነዉን የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም ይዘቶች ያብራሩት ክብርት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አይ ኤም ኤፍ በዚህ ረገድ ያለዉን ልምድና የቴክኒክ አቅም ለኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች እንዲዲያካፍል ጠይቀዋል፡፡ በኢኮኖሚ ስታትስቲክስ እንዲሁም በፐብሊክ ኢንቨስትመንት አስተዳደር ላይም የቴክነክ ድጋፍ በማድረግ በትብብር ለመስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡

የአለማቀፉ የገንዘብ ተቋም የኢትዮጵያ ተወካይ ቶቢያስ ናይቦ በበኩላቸዉ ተቋሙ ያለዉን ልምድና ተሞክሮ በማካፈል የትብብር ስራዉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

recent News
  • Image Here

    የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ከአለማቀፉ …

    04 April 2026
  • Image Here

    የግብርና ዘርፍ በአስር ዓመቱ የልማት ዕቅድ የመጀመሪያዎቹ 3 …

    04 April 2026
  • Image Here

    የፕላንና ልማት ሚኒሰቴር የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም …

    04 April 2026