ኢትዮጵያ በ20ኛው የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ጉባኤ ላይ ሁሉን ያሳተፈ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ እየተከተለች ያለውን ስትራቴጂ አቀረበች፡፡
**********************************************************************************************************************
አዲስ አበባ | ግንቦት 11/2017 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍጹም አሰፋ "በ20ኛው የአለም አቀፍ የሥራ ድርጅት የሥራ ላይ ተኮር ባለሙያዎች አህጉራዊ ጉባኤ" ላይ ኢትዮጵያ ሁሉን ያሳተፈ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ እየተከተለች ያለውን ስትራቴጂ በዝርዝር አቀረቡ።
ክብርት ዶ/ር ፍጹም ኢትዮጵያ የስራ ዕድል ፈጠራን፣ ክህሎት ማሳደግንና ስራ አጥነትን በመቅረፍ ላይ ትኩረት ያደረገ የ10-ዓመት የልማት እቅድ በመተግበር ላይ መሆኗን ገልፀዋል። በተለይም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ላይ እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች የስራ ዕድሎችን በመፍጠርና እንደ ወጣቶች ስራ አጥነትና የክህሎት አለመዛመድ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ መሆናቸውን አስረድተዋል።